Belay Bogale
12/09/2025
ሼር ሼር በተለይ መርሐቤቴዎች
ይህንን በፎቶ የምትመለከቱት ጀግና ኢትዮጵያዊ የቀድሞው ሰራዊት አባል የመረሐቤቴ ቤቴ ተወላጅ ባህርዳር በነበረበት ጊዜ መፀነስዋን እንኳን ያላወቃት ልጅ ተወልዳ አባቴ ወዴት ነው ያለሀው? ትላለች። በነገራችን ላይ ፈላጊዋ ያላትን መረጃ ሰጥታኛለች ስለዚህ ሌላ መረጃ የላትም እና "ቀበሌ ወረዳ እንደዚሁ EBS ትሂድ አትበሉ ምክንያቱም የወታደር ቤተሰብ አናጠያይቅም ብለው አቁመዋል። ለማንኛውም የዛሬ የአፋልጉኝ መረጃ
ተፈላጊው ወታደር ዘውዱ ፀጋዬ መሸሻ ወይም ማስረሻ ይባላል ። በደርግ ዘመነ መንግስት የኢትዮጵያ ወታደር ሆኖ ነብሮ ተብሎ ይጠራ በነበረው በ15ኛ ክ/ጦር ውስጥ ነበር።
ትውልዱ መረሐቤቴ ሲሆን በዛን ጊዜ አባቱ የቀበሌ ሊቀመንበር ነበር። አባቴ ከወላጅ እናቴ ወ/ት ባንቺአምላክ ቢያዝን ጋር የተዋወቁት ባህርዳር ቀበሌ 13 ጣና ሐይቅ ጀርባ በሚገኘው መኖርያ ቤታቸው ውስጥ ነው ።
በሰዓቱ እግሩን በጥይት ቆስሎ ተጎድቶ ነበር ። የህክምና ሞያ የነበራቸው አያቴ አቶ ቢያዝን ታከለ የአባቴን የቆሰለ እግሩን ይንከባከቡት ነበር ። በወቅቱ አባቴ ቤተኛ ሆኖ ከእናቴ ጋር የፍቅር ግንኙነት ጀምሮ በመሐከል እኔ መፀነሴንም ሳያውቅ ተለያዪ ። እናቴ ከአባቴ ጋር ለመጨረሻ ጊዜ የተያዩት መጋቢት 1982 ዓ.ም በባህርዳር ነው ። መረጃ ያላችሁ ወይም አባታችሁን የምታፋልጉ የቀድሞው ሰራዊት ቤተሰቦች የአባታችሁ የትግል ጓድ የሆነውን ወዲ ሻምበል በዚህ ስልክ +251 91 070 5777
ዋትስአፕ ላይ ልታገኙኝ ትችላላችሁ።
Click here to claim your Sponsored Listing.
Category
Contact the public figure
Telephone
Website
Address
3533 S Bennett Street
Seattle, WA
98118