ERSAS ART Studio
18/12/2025
እንኳን ደስ አለን !!🙏🏆
በ 7 ኛው 2025 የ ኳታር ዶሀ ኢንተርናሽናል አርት ፌስቲቫል ላይ ሀገሬ ኢትዮጵያን ወክዬ እጅግ ደስ የሚል ክብር እንደተቀናጀሁ ስነግራችሁ በኩራት ነው ፤
ኳታር ባዘጋጀችው 7ኛው አለም አቀፍ የ2025 የስነጥበብ ክንውን ላይ በርካታ የሀገሪቷ ባለስልጣናት፣ አምባሳደሮች ፣ዲፕሎማቶች በተገኙበት ከ70 በላይ ሀገራት ከ450 በላይ አለም አቀፍ ሠዓሊያን ፤ እኛም ኢትዮጵያን በመወከል ሠዓሊ ግርማ ቡልቲ፣ ሠዓሊ መስፍን መብራቱ፣ ሠዓሊ ቃለአብ አለማየሁ ሠዓሊ ረድኤት አካለወልድ እና የዴኮሬሽን ባለሙያ ለምለም በላይነህ እንዲሁም የዝግጅቱ አስተባባሪ ብራንድ አምባሳደር ሠዐሊ ተሰማ ተምትሜ ተሳትፈን ከፍ ያለ ክብር ተቅናጅተናል ::
ለዚህ ትልቅ ዝግጅት መሳካት ቅን የሆነው ሠዐሊ ተሰማ ተምትሜ ከነ ሙሉ ቤተሰቡ ላደረጋችሁት መልካም ተግባር እግዚአብሔር ይባርካችሁ::
ሁሌም አብረውኝ ስላሉ አመሰግናለሁ::
ሠዓሊ ዮሐንስ ባዩ
08/04/2025
“አርት ኦፍ ኢትዮጵያ 2025”
ከ ብዙዎች ዘንድ የደረስኩበት እና ለተከታታይ 6ተኛ ግዜ የ ቡድን ዐውደርዕይ የማቀርብበት “አርት ኦፍ ኢትዮጵያ” በ ሸራተን አዲስ ሆቴል ሚያዚያ 2 , 3 ( ሀሙስና አርብ ከ ጠዋቱ 4 ሰዐት - ምሽት 4 ሰዐት) ይካሄዳል እኔም የ ስዕል ስራዎቼም በ ቦታው እንገኛለን :: ይምጡ ይጎብኙ::
መግቢያውም በነፃ
🇪🇹
04/10/2024
የ ሰዐሊ ዮሐንስ ባዩ የ 10 አመት የ ስዕል ጉዞ ለማክበር “ምስጋና” በሚል ርዕስ ከ መስከረም 29 - ጥቅምት 1 / እረቡ : ሀሙስ : አርብ / ከጠዋቱ 3:00 - ማታ 3:00 ሰዐት በ ማሪዮት ሆቴል የ ስዕል አውደርዕይ አዘጋጅተናል:: እርሶም ይህንን የ ጥበብ ድግስ ተገኝተው ሀሴት እንዲያደርጉ ሰዐሊው ይጋብዛል::
መግቢያ :- በነፃ
ስለ ሰዐሊው መረጃ
https://t.me/Ersas_Studio
https://www.facebook.com/yohannes.ain
https://www.instagram.com/yohannes_bayou
#ኢትዮጵያ #ስዕል #ምስጋና
Click here to claim your Sponsored Listing.
Category
Culinary Team
Attire
Contact the public figure
Website
Address
Doha