Betel Set
Aziende Di Alimentari E Bevande nelle vicinanze
Via S. Maria a Cubito, 21, Cancello Ed Arnone
01/08/2023
የአማራ ክልል ወቅታዊ የሰላምና የፀጥታ ሁኔታዎች ላይ የሚመክር ውይይት በባህር ዳር ከተማ እየተካሄደ ነው
የአማራ ክልል ወቅታዊ የሰላምና የፀጥታ ሁኔታዎች ላይ የሚመክርና የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች የተሳተፉበት የውይይት መድረክ በባህር ዳር ከተማ እየተካሄደ ነው።
የአማራ ክልል መንግስት ኮሙኒኬሽን ቢሮ ሃላፊ አቶ ግዛቸው ሙሉነህ መድረኩን አስመልክቶ እንደገለፁት በክልሉ አንዳንድ አካባቢዎች የሚስተዋለውን የሰላም ችግር በጋራ ተወያይቶ መፍትሄ ለማምጣት ያለመ ውይይት ነው።
በአሁኑ ወቅት በክልሉ አንዳንድ አካባቢዎች የጸጥታ ችግር እና ህብትና ንብረት የማጥፋት ሁኔታዎች እየተስተዋሉ መሆናቸውን ገልፀዋል።
ከዚህ በተጨማሪም የጸጥታ ችግሩ በተለያዩ አካባቢዎች የልማትና የንግድ እንቅስቃሴዎችን በመግታት የክልሉን ህዝብ ወደባሰ ችግር ውስጥ እያስገባው መሆኑን አቶ ግዛቸው ተናግረዋል።
በመሆኑም እየተስተዋለ ያለውን ችግር በሰከነ መንገድ ለመፍታት ከክልሉ የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ጋር መወያየትና መመካከር አስፈላጊ ሆኖ መገኘቱን ገልጸዋል።
አቶ ግዛቸው እንዳሉት ውይይቱ ችግሩን በዘላቂነት ለመፍታት የሚያስችሉ መፍትሄዎችን በጋራ በማስቀመጥ የተጀመሩ የልማትና የለውጥ ስራዎች አጠናክሮ ለማስቀጠል የሚያግዝ ነው። ጥያቄዎችን በሰላማዊ መንገድ ተወያይቶ መፍታት እንደሚገባም አስገንዝበዋል።
የውይይቱ ተሳታፊዎችም በክልሉ የህግ የበላይነትን ለማረጋገጥ እየተሰራ ላለው ሥራ የሚኖራቸው ሚና የጎላ መሆኑን የገለጹት አቶ ግዛቸው፣ "በመድረኩም ችግሩን ለመፍታት የሚረዱ ግብአቶች ይገኛሉ ተብሎ ይጠበቃል" ብለዋል።
በውይይቱ ላይ በክልሉ ከሁሉም አካባቢዎች የተውጣጡ ከ400 በላይ የሃይማኖት አባቶች፣ የአገር ሽማግሌዎች፣ ተፅዕኖ ፈጣሪ ግለሰቦች እና ሌሎችም እየተሳተፉ ይገኛሉ።
•~•~•
"የጎሃ ቃልኪዳናችን የከፍታችን ልክ - ቃላችንን ፈፅመን ከፍታው ላይ እንገናኝ"
•~•~•
ለወቅታዊ ፣ ትክክለኛና አዳዲስ መረጃዎች የፓርቲያችንን የማህበራዊ ገፆች ይወዳጁ።
Clicca qui per richiedere la tua inserzione sponsorizzata.
Digitare
Sito Web
Indirizzo
Addis Abeba
Milan