Peps or coca
24/07/2024
ጎፋ ከአደጋው ማግሥት
ጎፋ፦በመሬት መንሸራተት አደጋው በአሁኑ ወቅት ከ40 በላይ የሚሆኑ ሰዎች ከአፈር በታች ይገኛሉ የሚል ጥርጣሬ መኖሩን የገዜ ጎፋ ወረዳ ባለሥልጣናት ዐሳውቀዋል ።
ከትናንት በስቲያ ሰኞ በደረሰው የመሬት መንሸራተት አደጋ 16 የቤተሰብ አባላቱን ያጣ፤ አምስት የባለቤታቸው ቤተሰብ አባላትን የቀበሩም አሉ።
አደጋውን አስከፊና በቃላት ለመግለጽ እንደሚከብድ የተናገሩት አቶ ዘለቀ « የቤተሰብ አባሎቻቸውን ከአፈር ናዳ ሥር ለማግኘት ያለውን ፈተና ከባድና የሚጨንቅ ነው ብለዋል።
ከተጫነው ናዳ ሥር የወጡ ሟቾች በጭቃ የተለወሱ ናቸው ። ሰዎች የቤተሰብ አባሎቻቸውን የሚለዩት የአስክሬኖችን ፊት በማጠብ ነው።
16 የቤተሰብ አባላቱን ያጣ ፣ ስምንት ልጆቿን ያጣች እናት አለች ፣ ቤተሰቦቹ አልቀውበት ብቻው የቀረ ሕጻንም አለ ፡፡ ሁኔታው ዘግናኝና አስጨናቂ ነው» ብለዋል ። በቀበሌው የደረሰው አደጋ ቁጥሩ ቢለያይም እያንዳንዱን ቤት ለከፋ ኃዘን መዳረጉን ተጎጂዎች ለዶቹ ቬለ ተናግረዋል ።
በመሬት መንሸራተት አደጋው ሕይወታቸው ያለፈ ቀሪ ሰዎችን የመፈለጉ ሂደት አሁንም መቀጠሉን የወረዳ የአደጋ ሥጋት ሥራ አመራር ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ ማስረሻ ማንአየ ለዶቼ ቬለ ገልጸዋል።
ሸዋንግዛው ወጋየሁ ዶቸ ቬለ
Click here to claim your Sponsored Listing.
Category
Culinary Team
Attire
Website
Address
Hawassa
Awassa