Hagere Community Development Association
Hagere Community Development Association (HCDA) is an indigenous non-governmental, non-profit, secular, legally registered association established in May 2012 with a group of volunteers who are committed for improving the livelihood of poor and vulnerable community groups. The founders have a wide experience in the area of community care services, social counseling and integrated community develop
28/02/2016
ከፕሮጀክቶቹ ውስጥም ዋና ዋናዎቹ
- በአፋር ክልል ዞን ሦስት ስር በሚገኙት ግዋኔ እና ቦርሞዳዪቱ ወረዳ ውስጥ ለሚገኙ 300 ወላጃቸውን ላጡ ህጻናት በተለያየ ሁኔታ ድጋፍ በማድረግ ትምህርታቸውን በአግባቡ እንዲከታተሉ አስተዋጽኦ ያበረከተ ሲሆን ከዚህ በተጨማሪ ለወላጆቻቸው(አሳዳጊዎቻቸው) አቅማቸውን ለማጎልበት በተለይ በኢኮኖሚ ራሳቸውን ችለው ልጆቻቸውን የሚያሳድጉበት መንገድ ለመፍጠር ዕቅድ ወጥኖ ያላሰለሰ ጥረት ሲያደርግ ቆይቷል፡፡
- በተመሳሳይ ሁኔታም ደቡብ ላይ በስልጤ ዞን ስር ከሚገኙ ወረዳዎች ሁለት ወረዳዎችን በመምረጥ ማለትም ከሁልባረግ እና ስልጤ ወረዳ ጋር በፕሮጀክት ርዕስ Educational material and clothing support for OVC students በተሰኘ ተፈራርሞ በአጠቃላይ ለ400 (አራት መቶ ) ወላጃቸውን ላጡ ህጻናት ድጋፍ እያደረገ ሲሆን በድምሩ በአሁን ሰዓት ደርጅቱ 700(ሰባት መቶ) ወላጃቸውን ላጡ ህጻናት እና ለአሳዳጊያቸው አስፈላጊውን ድጋፍ እያደረገ ይገኛል ፡፡
- ከዚህም በተጨማሪ በደቡብ ክልል በተወሰኑ ወረዳዎች የምግብ ዋሰትናቸውን ላላረጋገጡ የሕብረተሰብ ክፍሎች የምግብ አቅርቦት ስራ በሰፊው ሰርቷል፡፡
28/02/2016
ስለ ሀገሬ ኮሚዩኒቲ ደቨሎፕመንት አሶሴሽን
ሀገሬ ኮሚዩኒቲ ደቨሎፕመንት አሶሴሽን ለትርፍ ያልተቋቋመ መንግስታዊ ያልሆነ ሀገር በቀል ልማታዊ ድርጅት ነው፡፡ በዋነኛነት በሃገራችን ኢትዮጵያ ድህነትን በመቀነስ ረገድና በጎ አድራጎት መስኮች የአገሪቱን እቅዶች ግንዘቤ ውስጥ አስገብቶ በሁሉም መስክ የራሱን አሻራ ለማሳረፍ እየሰራ ይገኛል፡፡
ራዕይ /Vision/
ግንባር-ቀደም የልማት ድርጅት በመሆን በሀገሪቱ ዉስጥ የበለጸገ ፣ ንቁና የተማረ እንደዚሁም ከበሽታና ከድህነት የጸዳ ማህበረሰብ ተፈጥሮ ማየት፡፡
ተልዕኮ /Mission/
በሀገራችን ዉስጥ የድሆችንና ከከተማ የራቁ ማህበረሰቦችን አቅም በማሳደግ፣ መሰረታዊ የትምህርት፣ የጤና፣ እንደዚሁም የንጹህ ውሀ አቅርቦትን በማሳደግ ፣ በኤች ኤይ ቪ/ ኤድስና በቤተሰብ ምጣኔ ዙሪያ የግንዛቤ ማስጨበጫና የአቅም ግንባታ ስልጠናዎችን በማቅረብ፣ እንደዚሁም ተነሳሽነትን በመውሰድ የኢትዮጵያ የአየር ለውጥን በመንከባከብና በመጠበቅ በሁሉም መስክ የተሻለች ሀገር ሆና ማየት ነው፡፡
Click here to claim your Sponsored Listing.
Contact the school
Telephone
Website
Address
Addis Ababa
325