DireTube
11/06/2026
አዲሱ የተሽከርካሪ ሰሌዳ - ለአዲስ ተሽከርካሪዎች ብቻ ከዛሬ ጀምሮ እየተሰጠ ነው
🔴 የነባር ተሽከርካሪዎች መውሰጃ ጊዜ አልታወቀም፣
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከዛሬ ጀምሮ አዲሱ የተሽከርካሪ ሰሌዳ መሰጠት ጀምሯል።
የከተማዋ አሽከርካሪና ተሽከርካሪ ፈቃድና ቁጥጥር ባለስልጣን ዋና ሥራ አስኪያጅ ዘገየ በላይነህ በሰጡት መግለጫ እንዳሉት ፥ ከሴኔ 4 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ አዲሱ ሰሌዳ ለከተማዋ ተሽከርካሪዎች መሰጠት ተጀምሯል።
በዚህ መሰረትም ተመዝግበው ሲጠባበቁ የነበሩ አሽከርካሪዎች በተመዘገቡበት ቅርንጫፍ በኩል ስልክ ተደውሎ እንዲወስዱ ይደረጋል ብለዋል።
አዲሱ ሰሌዳ የሚሰጠው ለአዳዲስ ተሽከርካሪዎች ብቻ መሆኑንም ነው ዋና ሥራ አስኪያጁ ያስገነዘቡት፡፡
ነባሩን የተሽከርካሪ ሰሌዳ የሚጠቀሙትን በተመለከተ ወደፊት በትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር በኩል ይፋ እንደሚደረግ አመልክተዋል፡፡
Want your business to be the top-listed Media Company in Addis Ababa?
Click here to claim your Sponsored Listing.
Click here to claim your Sponsored Listing.
Category
Contact the business
Website
Address
Addis Ababa