Addis Ababa Police
Values: Professionalism, Integrity, Respect for diversity, Respect for Human rights በጀግንነት መጠበቅ፤በሰብዓዊነት ማገልገልⵑ (Protect With Courage, Serve with Compassionⵑ)
እሴቶቻችን
ብዛህነትን ማክበር (Respect for Diversity)
ሙያዊ ብቃት (Professionalism)
ምሉዕነት ( Integrity )
ሰብዓዊ መብት ማክበር (Respect for Human Rights)
29/05/2026
የመኪና እቃ ስርቆት ወንጀል የፈፀመው ተከሳሽ በፅኑ እስራት ተቀጣ።
***
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 21 ቀን 2018 ዓ/ም (አዲስ ፖሊስ)፦ ተከሳሽ አቡበከር ሰይፈ የስርቆት ወንጀሉን የፈፀመው በኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ ወረዳ 4 አካባቢ ነው።
የግል ተበዳይ የሰሌዳ ቁጥር ኮድ -2C-77538 አ/አ የሆነ BYD የኤሌክትሪክ መኪና በመኖሪያ ቤታቸው አካባቢ አቁመው በሄዱበት አጋጣሚ ተከሳሽ 130 ሺህ ብር የሚገመት የቻርጅ ማድረጊያ ክዳንና 41 ሺህ ብር የሚያወጣ የግራ ስፖኪዮ በአጠቃላይ 171 ሺህ ብር ግምት ያለው ንብረት ከተሽከርካሪው ላይ ገንጥሎ ለማምለጥ ሲሞክር ስራ ላይ በነበሩ የፖሊስ አባላትና በህብረተሰቡ ትብብር እጅ ከፈንጅ መያዙን በክፍለ ከተማው ፖሊስ ዋና መምሪያ የአለም ባንክ አካባቢ ፖሊስ ጣቢያ አስታውቋል።
በተከሳሽ አቡበከር ላይ አስፈላጊውን ምርመራ ሲያጣራ የቆየው የአለም ባንክ አካባቢ ፖሊስ ጣቢያ መዝገቡን ለዐ/ህግ በማቅረብ ክስ እንዲመሰረትበትም አድርጓል፡፡
የፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ኮልፌ ቀራንዮ ምድብ የወንጀል ችሎት ተጣርቶ የቀረበለትን መዝገብ በማጤን ተከሳሽ ጥፋተኝነቱን በሰው ማስረጃዎች ካረጋገጠ በኋላ ተከሳሹን ያስተምራል ሌሎችንም ያስጠነቅቃል ሲል በ4 ዓመት ፅኑ እስራት እንዲቀጣ ውሳኔ እንዳስተላለፈበት ገልጿል።
የተሽከርካሪ ባለ ንብረቶች መኪና አቁመው በሚሄዱበት ወቅት ለወንጀል ፈፃሚዎች ምቹ ሁኔታን በማይፈጥር መልኩና በቂ ጥበቃ ባለበት ቦታ አቁመው መሄድ እንዳለባቸው ያሳሰበው የአዲስ አበባ ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ ወንጀል ከተፈፀመም በአፋጣኝ ለአቅራቢያ ፖሊስ ጣቢያ በማመልከት ወንጀል ፈፃሚዎች ተይዘው በህግ አግባብ እንዲቀጡ ማድረግ እንደሚገባ መልዕክቱን አስተላልፏል።
*
ዘገባ ፦ ረ/ኢንስፔክተር ዘላለም አበበ
*
ለፖሊሳዊ መረጃዎቻችን፦
በፌስቡክ :- https://www.facebook.com/Addisababapolice
በቴሌግራም:- https://t.me/addispolice
በዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/AddisAbabaPoliceCommission
በትዊተር፦Twitter https://twitter.com/AddisPolice
ድረ ገጽ፦ web https://www.addispolice.gov.et/
“በጀግንነት መጠበቅ በሰብዓዊነት ማገልገል!”
Click here to claim your Sponsored Listing.
Category
Contact the organization
Telephone
Website
Address
Arada Sub City , Addis Ababa Police
Addis Ababa
5647