MFM
የመካነ ሰላም ኤፍ ኤም በቅርቡ በመካነ ሰላም ከተማ የኤፍ ኤም ሬድዮ ስርጭት ይጀምራል።
በፌስቡክ ፣ በቴግራም አካባቢያዊ ፣ ክልላዊ ፣ ሀገራዊ እና አለም አቀፋዊ ዘገባዎችን በፍጥነት ለማህበረሰቡ ያቀርባል።
MFM ለማህበረሰብ ፍትህ
በዩቱብ እና በቲክቶክም ይወዳጁን
https://t.me/mekaneselamfm
29/05/2026
MFM-NEWS || የኬንያ ከፍተኛ ፍርድ ቤት የአሜሪካ የኢቦላ ተጋላጭ ኳራንታይን ማዕከል ስምምነትን በጊዜያዊነት አገደ!
የኬንያ ከፍተኛ ፍርድ ቤት፣ አሜሪካ በምስራቅ አፍሪካ ለዜጎቿ ልታቋቁመው ያሰበችውን አስገዳጅ የኢቦላ ኳራንቲን ማዕከል ዕቅድ በጊዜያዊነት አግዷል። የከፍተኛው ፍርድ ቤት ዳኛ ፓትሪሺያ ኛውንዲ (Patricia Nyaundi) አርብ ዕለት በሰጡት አስቸኳይ ትዕዛዝ፣ ይፋዊ ያልሆነውና የአካባቢው የጤና ባለሙያዎችና የሰብዓዊ መብት ተሟጋቾችን ክፉኛ ያስቆጣው ስምምነት ላይ ሙሉ እገዳ የጣሉ ሲሆን፤ ጉዳዩን አስመልክቶ የቀረበው የካቲባ ኢንስቲትዩት (Katiba Institute) የተባለው የህግ ተሟጋች ድርጅት አቤቱታ በቀጣዩ ሳምንት ሙሉ የፍርድ ቤት ክርክር እንደሚደረግበት ታውቋል።
ይህ አወዛጋቢ ስምምነት ይፋ የሆነው በዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ እና በኡጋንዳ በተከሰተው የኢቦላ ወረርሽኝ ምክንያት ዓለም አቀፍ ስጋት በረታበት ወቅት ነው። አሜሪካ የላቀ የጤና መሠረተ ልማት እያላት ለበሽታው የተጋለጡ ዜጎቿን ወደ ራሷ ምድር ወስዳ ከማከም ይልቅ፣ በኬንያ ወታደራዊ ጣቢያ (Laikipia Air Base) ላይ በምስጢር በተሰራ ባለ 50 አልጋ ማዕከል ውስጥ ለማቆየት መምረጧ የአገር ውስጥ የሕክምና ባለሙያዎችንና ተሟጋቾችን በጽኑ አስቆጥቷል። የኬንያ የህክምና ባለሙያዎች ማህበር የኬንያ መንግስት የስምምነቱን ዝርዝር በአስቸኳይ ይፋ ካላደረገ የስራ ማቆም አድማ እንደሚያደርግ አስጠንቅቋል።
የአገር ውስጥ ተሟጋቾች ድርጊቱን "አፍሪካን የአሜሪካ የኢቦላ በሽተኞች መጣያ የማድረግ አዲስ የቅኝ ግዛት አስተሳሰብ ነው" በሚል የኮነኑት ሲሆን፣ ምዕራባውያን የራሳቸውን ህዝብ ከባዮሎጂያዊ አደጋ ለመጠበቅ ሲሉ አፍሪካን እንደ መከላከያ ጋሻ (Buffer Zone) እየተጠቀሙባት መሆኑን ገልጸዋል። ምንም እንኳን የአሜሪካ መንግስት ወረርሽኙ ወደ ባህር ዳርቻው እንዳይደርስ መከላከል ቀዳሚ ምርጫው መሆኑን ቢገልጽም፣ የኬንያ ዜጎች ግን ሉዓላዊነትና የህዝብ ጤና በገንዘብ እንደማይለወጥ በመግለጽ ዕቅዱን በከፍተኛ ሁኔታ እየተቃወሙት ይገኛሉ።
ለሌሎችም መረጃዎች በቴሌግራም ይወዳጁን https://t.me/mekaneselamfm
27/05/2026
በመካ ከተማ በሚገኘው ታላቁ መስጊድ በ1447ኛ የኢድ አል አድሃ ሶላት ላይ ከ1,7 ሚሊዮን በላይ ምዕምናን ተሳትፈዋል
Click here to claim your Sponsored Listing.
Category
Telephone
Website
Address
Addis Ababa
KELIFFABUSSINESCENTER