Ethio-Fact

Ethio-Fact

Share

16/08/2023

ከአማራ ክልል አመጽ በስተጀርባ በግንባር ቀደምነት ያሉት ሰው አቶ ገዱ አንዳርጋቸው መሆናቸው አሁን ግልፅ ሆኗል።

👉አቶ ገዱ እንዳሉት ከሦስት ወር በፊት መከላከያ በክልሉ ሕዝብ ዘንድ መልካም እይታ ነበረው፤ እውነታው ግን ይህ ጃውሳ ሃይል በመከላከያ ላይ ቃታ መሳብ ከጀመረ ድፍን ሁለት አመት መሆኑ ነው።

አቶ ገዱ መከላከያ ያለምንም ቅድመ ሁኔታ ወደ ካንፑ ይመለስ ብለዋል። ለመሆኑ ጃውሳው ሃይል በሁሉም የአማራ ክልል ከተሞች

👉የመከላከያን ካምፖች ከቦ ጥቃት ሲፈጽም፣
👉ወይን ቤቶችን ሰብሮ እስረኞችን ሲያስፈታ፣
👉የመሳሪያ ግምጃ ቤቶችን ሲዘርፍ
👉የፖሊስ ማሰልጠኛ ኮሌጆችን ሲያወድም
👉የመንግስት መዋቅሮችን ሲያፈርስ
👉የግል እና የመንግስት ተቋማትን ሲዘርፍ
👉አድባራት እና ገዳማትን የጦር መሳሪያ ዴፖ ሲያደርግ

አንድ ቃል ያልተነፈሱት፣ እንደውም እንደህዝባዊ አመፅ እና ትክክለኛ እርምጃ ቆጥረው በተቃራኒው መንግስትን እንደጥፋተኛ ሲቆጥሩ መስማት ክልሉን ሲያስተዳድሩ ከነበሩ ሰው የማይጠበቅ ብቻ ሳይሆን አሳዛኝም ጭምር ነው።

እኝህ ሰው በተደጋጋሚ የሚኮንኑት ብልጽግና ፓርቲ የአባልነት መልቀቂያ አስገብተዋል? ብልጽግናን ወክለው አይደለምን የተወዳደሩት? አቶ ገዱ በብልጽግና ማሊያ ለጃውሳው ሲጫወቱ እንደማየት ትልቅ ቅሌት የለም።

#ጃውሳ

Want your public figure to be the top-listed Public Figure in Addis Ababa?
Click here to claim your Sponsored Listing.

Category

Website

Address


Addis Ababa