ebro

ebro

Share

07/03/2026

ሰበር መረጃ

የኢራን እስላማዊ አብዮታዊ ዘብ በሆርሙዝ ወሽመጥ በኩል ለማለፍ የሞከረች ነዳጅ ጫኝ መርከብ መምታቱን አስታወቀ፡፡

አብዮታዊ ዘቡ በቴሌግራም ቻናሉ አመሻሹን ባሰራጨው መረጃ "ፕሪማ" የሚል ስያሜ የነበራት ነዳጅ ጫኝ መርከብ በወሽመጡ በኩል “መተላለፍ እንደማይቻል" የተሰጠውን 'ተደጋጋሚ ማስጠንቀቂያ' ችላ በማለቷ በድሮን መመታቷን ገልጿል።

ሰሞኑን የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ “አስፈለጊ ከሆነ” የአሜሪካ ባሕር ኃይል በዚያ የሚያልፉ መርከቦችን እንደሚያጅብ ተናግረው የነበረ ቢሆንም እስከአሁን ተግባራዊ ማድረግ አልቻሉም።

ለተለያዩ መረጃዎች ቤቱን ፎሎ በማድረግ ቤተሰብ ይሁኑ እናመሰግናለን ....

03/03/2026

ሰበር ዜና፣ የኢራን መንግሥት በታሪኩ እጅግ አስቸጋሪ በሆነው የህልውና ፈተና ውስጥ ሆኖ የሥልጣን ሽግግር ለማድረግ እየታገተ መሆኑን ያሳያል። የፋርስ የዜና ወኪል (Fars News Agency) እንደዘገበው፣ የባለሙያዎች ምክር ቤት (Assembly of Experts) የአያቶላ አሊ ኻሜኒን ተተኪ ለመሰየም የመጨረሻውን ድምፅ አሰጣጥ እያከናወነ ይገኛል።

​ይህ ስብሰባ እየተካሄደ ያለው ቀደም ሲል እስራኤል በምክር ቤቱ ስብሰባ ላይ ጥቃት ሰንዝራለች ከተባለበት አስፈሪ ድባብ ውስጥ ሆኖ መሆኑ፣ የኢራን አመራር "አልሸነፍም" ባይነትን ለማሳየት እያደረገው ያለውን የመጨረሻ ሙከራ ያሳያል። በሌላ በኩል፣ የተገደሉት መሪ አያቶላ አሊ ኻሜኒ የቀብር ሥነ-ሥርዓት በሰሜን ምስራቅ ኢራን በምትገኘው መሽሃድ (Mashhad) ከተማ እንደሚፈጸም ታውቋል። መሽሃድ ለሺዓ ሙስሊሞች የተቀደሰች ስፍራ መሆኗ፣ የቀብር ሥነ-ሥርዓቱ ሕዝባዊ ስሜትን ለመቀስቀስና ለወታደራዊ ግዳጅ አዲስ ወኔ ለመፍጠር የታለመ ስትራቴጂካዊ ውሳኔ ይመስላል።

03/03/2026
03/03/2026

🚨🚨ሰበር ዜና፦ አሜሪካ የቶማሃውክ (Tomahawk) መርከብ አጥፊ ሚሳይሎችን በኢራን ላይ ተኮሰች።

ከየካቲት 21 (Feb 28) ጀምሮ እየተካሄደ ባለውና "ኦፕሬሽን ኤፒክ ፊውሪ" (Operation Epic Fury) ተብሎ በተሰየመው ወታደራዊ ዘመቻ፣ የአሜሪካ ባህር ኃይል መርከቦች የቶማሃውክ (Tomahawk) ሚሳይሎችን በኢራን ወታደራዊ ኢላማዎች ላይ ተኩሰዋል። ሮይተርስ፣ ሲኤንኤን እና ሴንትኮም (CENTCOM) የተፈጸሙትን የአየር ድብደባዎች የሚያሳዩ ምስሎችንና ቪዲዮዎችን በማያያዝ መረጃውን አረጋግጠዋል።

Via BRICS News

Photos from ebro's post 01/03/2026

>

ከዳግማዊ አፄ ምኒሊክ ሐውልት ግርጌ ላይ በፅሁፍ የተቀረፀው ዘመን የማይሽረው ድንቅ ጥቅስ ፤

ክብርና ሞገስ ከወራሪ ነፃ የሆነች ሀገር ላስረከቡን ጀግኖች አርበኞቻችን 🙏💚💛❤️

#አድዋ

Want your business to be the top-listed Grocery Store in Addis Ababa?
Click here to claim your Sponsored Listing.

Category

Website

Address


Addis Ababa
Addis Ababa
1000