PICE
21/05/2026
በ16ኛው የቴክኖሎጂ ሳምንት ላቅ ያለ ውጤት ላስመዘገቡ አካላት የምስክር ወረቀት ተበረከተ
አዲስ አበባ —
ግንቦት 2018 ዓ.ም
በ2018 በጀት ዓመት በከተማ አቀፍ በተካሄደው 16ኛው የቴክኖሎጂ ሳምንት ላይ ማዕከሉን ወክለው ተሳትፎ ለነበራቸውና ከፍተኛ አስተዋጽኦ ላሳዩ የማዕከሉ አሰልጣኞች የዕውቅና እና የምስጋና ወረቀት የመበርከት ሥነ-ሥርዓት ተካሄደ።
በዕለቱ በተከናወነው መርሀግብር ላይ በቴክኖሎጂ ሳምንቱ ላይ የተለያዩ የፈጠራ ፕሮጀክቶችን ለሰሩ እና ላቀረቡ ባለሙያዎች የምስክር ወረቀት የተበረከተላቸው ሲሆን፣ በተመሳሳይ መልኩ በተግባራዊ ጥናትና ምርምር ዘርፍ ላይ ማዕከሉን በመወከል በውድድሩ ላይ ለተሳተፉና ላቅ ያለ አስተዋጽኦ ላበረከቱ አካላትም የምስጋና ወረቀት ተበርክቶላቸዋል።
የዕለቱን መርሀግብር በመምራት የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የቴክኖሎጂ ልማትና ኢንኩቤሽን ም/ዲን አቶ ተስፋዬ ወርቁ ማዕከሉ በቴክኖሎጂ ሳምንት ላይ ባሳየው እጅግ ከፍተኛ ተሳትፎና ባስመዘገበው ውጤት ምክንያት የዋንጫ ሽልማትና የምስክር ወረቀት እንደተበረከተለት ገልጸዋል።
የመርሀግብሩ ማጠቃለያ ላይ የማዕከሉ ዋና ዲን አቶ አድማሱ በቀለ ባስተላለፉት መልዕክት፣ ይህ ታላቅ ውጤት ሊመዘገብ የቻለው በግለሰብ ጥረት ብቻ ሳይሆን በማዕከሉ ውስጥ የሚገኙ መላው አካላት በጋራና በህብረት በመስራታቸው መሆኑን አውስተዋል። ዋና ዲኑ አክለውም ይህ ስኬት እንዲመጣ የበኩላቸውን አስተዋጽኦ ላበረከቱ የማዕከሉ አባላት በሙሉ ያላቸውን ጥልቅ ምስጋናና አክብሮት አቅርበዋል።
የልህቀት ማዕከሉ የሶሻል ሚዲያ ፕላት ፎርሞችን በመቀላቀል ቤተሰብ ይሁኑ
Websit ....
https://pice.sims.aatvetb.edu.et/
Telegram Channel …….PICE (https://t.me/pice1962)
YOUTUBE Channel ……. PICE1962
(https://www.youtube.com/)
Facebook Channel ………….PICE
(https://m.facebook.com/edu.pice.et/)
TikTok Channel ………Pice_1962
(https://www.tiktok.com/)
የወርቅ ማጣሪያ
16ኛው የቴክኖሎጂ ሳምንት
16 ኛው ከተማ አቀፍ የቴክኖሎጂ ሳምንት
የቴክኖሎጂ ልህቀት ለሀገር ብልፅግና በሚል መሪቃል በልህቀት ማዕከሉ እየተከበረ ይገኛል፡፡
Click here to claim your Sponsored Listing.
Category
Contact the school
Website
Address
Https://goo. Gl/maps/pRCrxGcKvqhzPxVB 6
Addis Ababa
Opening Hours
| Monday | 02:00 - 17:00 |
| Tuesday | 02:00 - 17:00 |
| Wednesday | 02:00 - 17:00 |
| Thursday | 02:00 - 17:00 |
| Friday | 02:00 - 17:00 |