BMB TUBE

BMB TUBE

Share

Photos from BMB TUBE's post 19/02/2025

“ እናቴን በሕይወት ባጣም ሌሎች ኢትዮጵያዊያን እናቶቼ ያላችሁን በማገዝ ከሞት ታደጉኝ ” - የ16 ዓመቷ የልብ ታማሚ

በጸጥታ ችግር ከወለጋ ተፈናቅላ በደብረ ብርሃን ቻይና መጠለያ ካምፕ ከገባች አራት አመት እንዳስቆጠረች የገለጸችው የ16 ዓመት ታዳጊ ለቀዶ ጥገና ከፍተኛ ገንዘብ በመጠየቋ እርዳታ እንዲረግላት ተማጸነች።

በቶሎ ካልታከመች ሕይወቷ ከባድ አደጋ ላይ መሆኑን እንደተነገራት ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ቃሏን የሰጠችው ታዳጊዋ፣ ለህክምናው ወጪ 783 ሺሕ ብር እንደተጠየቀች፣ ገንዘቡን ማግኘት እንዳልቻለች አስረድታለች።

“እናቴ ሞታለች። የወለጋ ተፈናቃይ ነኝ። ሀኪም ‘የልብሽ የደም ማስተላለፊያ አብጧል’ አለኝ” ያለችው ታማሚዋ፣ በሕይወት ያሉት ቤተሰቦቿም በጸጥታው ችግር ቤት ንብረታቸውን ትተው ተፈናቃይ መሆናቸውን ተናግራለች።

እርዳታ ጠያቂዋ ታዳጊ ሀያት በላይ፣ “እናቴን በሕይወት ባጣም ሌሎች ኢትዮጵያዊያን እናቶቼ ያላችሁን በማገዝ ከሞት ታደጉኝ” ስትል ተማጽናለች።

የታማሚዋ ቤተሰቦችም፣ ታዳጊ ሀያት ህመሙ ከጀመራት ሰባት አመታትን እንዳስቆጠረች፣ በቻሉት መጠን ህክምና እየተከታተለች ብትቆይም መፍትሄ ሳታገኝ እንደቆየች ገልጸው፣ ልበ ቀናዎች እንዲረዷቸው ጠይቀዋል።

መርዳት ለምትሹ፣ 1000628382895 የታማሚዋ እህት ፋጡማ አሊ ሁሴን የንግድ ባንክ ሒሳብ ቁጥር ነው።

ደውሎ ለመጠየቅ፣ በ0945667806 ታማሚዋን፣ በ0921195123 ወንድሟን፣ 0955581772 እህቷን ፋጡማ አሊን ማግኘት ይቻላል።

👉

Photos from BMB TUBE's post 18/02/2025

ሰበር መረጃ‼️
በግብፅ እና በእስራኤል መካከል ትልቅ ጦርነት በማንኛውም ሰአት ሊፈነዳ ይችላል ሲሉ የእስራኤል አምባሳደር ተናገሩ‼️
በአሜሪካ የእስራኤል አምባሳደር ግብፅ የሰላም ስምምነቱን በእጅጉ እየጣሰች ነው ብለዋል። በቅርቡ በግብፅ ላይ እርምጃ እንወስዳለን ሲሉ በዛሬው እለት ዝተዋል።

አክለው የተናገሩት በአሜሪካ የእስራኤል አምባሳደር ዬቺኤል ሊተር ግብፅ ኢንተርኔቱን እና ሶሻል ሚዲያውን በግብፅ ጦር ምስሎች አጥለቅልቃው እየተመለከትን ነው ሲሉ ከሰዋል።
በግብፅ በኩል ያልተለመደ የተባለለት ሰሞንኛ ክስተት የተስተዋለው በተለይም የግብፅ ፓራትሮፐር ብርጌዶች በኦክቶበር 7 ሐማስ ጥቅም ላይ ያዋለውን አይነት የአውሮፕላን ዝላዮች እና ኦፕሬሽኖችን ጨምሮ የተቀናጀ ነው የተባለለትን የወታደራዊ ስልጠና ልምምዶችን የሚያካሂዱበት ተንቀሳቃሽ ምስል በስፋት መዳረሱን ተከትሎ ነው።
ለጥቆማና ማስታወቂያ ለማሰራት
👉

18/02/2025

#ያሳፍራል😭😭 ምን አይነት ሰዎች ትሆኑ??

ይህች ታዳጊ ትባላለች!የ9ኛ ክፍል ተማሪ ናት!በጣም የምትወደው አባቷን በአንድ ቀን ህመም በድንገት በሞት ካጣች 7ወር ሆኗታል!

እሮብ የካቲት5 ምንም ነገር ሳትናገር ቃሊቲ አካባቢ ከሚገኘው ቤታቸው ድንገት ወጥታ ጠፍታ እናት በለቅሶና በመንከራተት ለቀናት እየፈለገቻት ትላንት እሁድ የካቲት9 በ0920751657 አንድ ስልክ ይደወልላታል:-

"ፖሊስ ነኝ፣የምደውለው ከአዳማ ነው፣ልጅሽ ከመኪና ላይ ልጆች ወርውረዋት በጣም ተጎድታለች፣ ጭንቅላቷ ውስጥ ደም ፈሷል፣አሁን የምትገኘው አዳማ አጠቃላይ ሆስፒታል ነው ሪፈር ወደ አዲስ አበባ ተፅፎላታል፣...." እያላት እናት ተደናግጣ በእንባ ማውራት ስላልቻለች ልጇ ሙሉቀን ስልኩን ይቀበላታል!
ምንድነው ሲላቸው?"በህይወት እንድትተርፍ በግል ትራንስፖርትም ቢሆን በአስቸኳይ ወደ አዲስ አበባ መምጣት አለባት"ብሎ የሹፌር ስልክ ሰጣቸው፣

ሹፌር ነኝ ባዩ በ0951948455 ደውሎ በ3000ብር ተስማምቶ ፅዮን አብርሀም በሚል ቴሌብር ብሩን እንዲያስገቡ አስጠንቅቆ በመጨረሻም መንገድ እንደጀመሩና ጥቁር አንበሳ እንዲጠብቁት ነግሯቸው ወዲያውኑ ጎረቤት ወዳጅ ዘመድ ተጨማምረው እያለቀሱ ጥቁር አንበሳ ሆስፒታል ደረሱ!!

ከደቂቃዎች በኋላ "የት ደረሳችሁ?" ለማለት ስልክ ሲደውሉ ዝግ ሆነ፣ፖሊስ የተባለው ጋርም ሲሞክሩ አይሰራም፣እንደገና ደውለው ጎማቸው እንደተበላሸና በሌላ መኪና እንዲመጡ ገንዘብ እንዲልኩላቸው ሲጠይቋቸው እያታለሏቸው ሊሆን እንደሚችል ጠረጠሩ!አዳማ ያለ ዘመድ ጋር ደውለው ወደ ሆስፒታል ሲሄዱ በዕለቱ የተመዘገበ አደጋ እንደሌለና እንዲህ የምትባልም ታማሚ እንደሌለች ሰሙ!!ጉዳዩ ሿሿ እንደሆነ አወቁ‼️

አስቡት በጭንቀታችሁ ላይ ገንዘብ ለማግኘት ብለው በውሸት ፈጠራ ወሬ ሌላን ሰው ለማሳመምና ለመግደል የሚሞክሩ እንደነዚህ ያሉ ብዙ ነውረኞች አሉ! #ተጠንቀቁ🙏 ልቧ የተሰበረው እናት #ሼር በማድረግና በፀሎት ቢያንስ የጠፋችውን ልጇን በማገናኘት ወደ ሳቋ እንመልሳት🙏 እናንተ ነውረኞችም የትም አታመልጡም!
"ለመልካም ስራ ረፍዶ አያውቅም"

0913151226-
0912072849

👉

17/02/2025

የ12 አመት ታዳጊ ጠልፎ ለመሄድ የሞከረው ግለሰብ በህዝብ ጥቆማ በቁጥጥር ስር መዋሉን የለጋምቦ ወረዳ ፖሊስ አስታወቀ፡፡

በለጋምቦ ወረዳ ፖሊስ ጽ/ቤት የወንጀል ምርመራ ክፍል ተወካይ ዋና ሳጂን እንድሪስ ሁሴን እንደገለጹት መነሻውን ከከላላ ወረዳ መድረሻውን ደሴ ከተማ ያደረገው የህዝብ ማመላለሻ አውቶቡስ የካቲት 9/2017ዓ.ም ከጧቱ 12፡00 ስዓት ተከሳሽ ሁሴን አሊ የ12ኣመቷን ታደጊ ሀውለት ታደሰ አሰን የተባለችውን ህፃን ከመነሀሪያ ውጪ አሳፍሮ ወደ ደሴ ለመውሰድ ሲሞክር ተሳፈሪው ህብረተሰብ በሁለቱ መካከል የታየውን ልዩነት በመጠራጠር አቀስታ ከተማ ሲደርስ በከተማው ለሚንቀሳቀሱት ሰላም አስከባሪዎች ና ፖሊሶች ማስረከብ ተችሏል ብለዋል፡፡

ተከሳሽ ሁሴን አሊ የከለላ ወረዳ 01 አቤት ውሃ ነዋሪ ሲሆን በከላላ ከተማ እራሱን የሀይማኖት መሪ /ሸህ/እና ደረሳ በማስመሰል ሲኖር ቆይቶ ታዳጊ ሀውለት ታደሰ አሰንን ከከላላ ወረዳ 02 ቀበሌ ቀርቀሬ ከምትባል ቦታ ፍየልና ከብት ከምትጠብቅበት የካቲት 8/2017ዓ.ም ከቀኑ11 ፡00 ከተናገርሽ አርድሻለሁ፣ እገልሻለሁ በማለት አስፈራርቶ አክስቱ ቤት በማሳደር ሊሰወር ሲሞክር መያዙን ገልጸዋል፡፡

ታዳጊዋ ጉዳት ሳይደርስባት እንድትገኝና ወንጀለኛውም በቁጥጥር ስር እንድውል ያደረገውን የአውቶቡስ ተሳፋሪ የከለላ ወረዳ ህዝብ እያመሰገን ሁሉም ህብረተሰብ ወንጀልን በማጋለጥ ተባባሪነቱን አጠናክሮ እንድቀጥል ሲሉ መልእክታቸውን አስተላልፈዋል፡፡ ታዳጊዋን ለቤተሰቦቿና ተከሳሹን ለከላላ ወረዳ ፖሊስ እንደሚያስረክቡ ዋና ሳጂ እንደሪስ ሁሴን ገልጸዋል፡፡

የለጋምቦ ወረዳ ኮሙዩኒኬሽን
👉

Want your business to be the top-listed Computer & Electronics Service in Addis Ababa?
Click here to claim your Sponsored Listing.

Address


Addis Ababa