EthioTimes
06/06/2026
ኮሜዲያን አሌክስ ፈጣሪ ይማርህ‼️
(ዘሪሁን ተዝናኑ)
በስታንዳፕ ኮሜዲ ስራዎቹ በርካታ ስራዎችን
ያበረከተልን ፣ ዋሸው እንዴ የተሰኘው ፕሮግራም
ከመስራቾቹ አንዱና አቅራቢ ፣ አርትስ ቲቪ ላይ
የ90ዎቹን ፕሮግራምን የመራ ፣ በቅርቡም
ኢቢኤስ ቲቪ ላይ የቤተሰብ ጨዋታን ለመምራት
የተወዳደረና ብቃቱን ያሳየን ፦
ጨዋታ አዋቂው ፣ ጥርስ የማያስከድነው
እጅግ ሰው አክባሪው
ኮሜዲያን አሌክስ በጠና ታሞ
ራስ ደስታ ሆስፒታል ድንገተኛ ክፍል ይገኛል።
ፈጣሪ ለቤተሰቦቹ ፣ ለሚወዳቸው ልጆቹ ሲል
ምህረቱን ይላክለት።
ቤተሰቦቹ ፣ ወዳጅ አድናቂዎቹ በፀሎታችሁ አስቡት !
አሌክስ አይዞን የምታምነው ፈጣሪ ይምርሃል።
አክባሪና አድናቂ ወንድምህ
ዘሪሁን ተዝናኑ !!!
06/06/2026
ዛሬ በአዲስአበባ ስታዲየም ሊደረግ በነበረው የአርሰናል ደጋፊዎች ኮንሰርት በአርሲ ኦርቶዶክሳዉያን ጭ*ፍጨፋ ምክንያት ከፕሮግራሙ እንደማይገኝ አርቲስት ሳሚ ዳን ገልጿል።
06/06/2026
"ክብርት ከንተባ አዳነች አቤቤን አመስግኑልኝ" ጋዜጠኛ ኤሊያስ መሰረት
👇👇👇
"ከንቲባ አዳነች አቤቤ በትውልድ ስፍራቸው ከሰሞኑ የተከሰተው አሳዛኝ እና አሰቃቂ ግድያ እንዳይስፋፋ ከአሰኮ ወረዳ አስተዳዳሪ አቶ ገቢ ገልቹ ጋር በአንድነት በመሆን እያደረጉ ያለው ጥረት ከፍ ያለ በመሆኑ የላቀ ምስጋና ይገባቸዋል። ሁሉም መረጃ ለሚድያ ፍጆታ አይውልም እንጂ ዝርዝሩ ብዙ ነው፣ ችግሮች አሁንም ቢኖሩም ከትናንት ጠዋት ጀምሮ በአካባቢው መረጋጋት እንዳለ መረጃዎች አሰባስቤያለሁ።
ከዚህ ጋር ተያይዞ የወረዳው ፖሊስ አዛዥ አቶ አባቡ አብደላ በቁጥጥር ስር የዋሉ ሲሆን የሰላምና ፀጥታ ሀላፊው ደግሞ ለግዜው ተሰውረዋል፣ ያሉበት አልታወቀም።
በተቃራኒው የክልሉ ልሳን የሆነው ኦቢኤን (OBN) ከዛሬ ጠዋት ገደማ ጀምሮ ጋዜጠኞቹን ወደ ስፍራው በማሰማራት ዶክመንታሪ ማሰራት ጀምሯል፣ ዶክመንታሪው ላይ የመንግስት ሰራተኞችን ጭምር የአካባቢው አርሶ አደር አስመስሎ በማቅረብ እየተሰራ እንደሆነ መረጃ ደርሶኛል።
ይሁ ሁሉ ግን ለምን?
ለሌላ እልቂት ዝግጅት?
ከንቲባዋን ግን ለጥረታቸው አመስግኑልኝ!"
Click here to claim your Sponsored Listing.
Category
Contact the business
Website
Address
Opening Hours
| Monday | 9am - 5pm |
| Tuesday | 9am - 5pm |
| Wednesday | 9am - 5pm |
| Thursday | 9am - 5pm |
| Friday | 9am - 5pm |
| Saturday | 9am - 5pm |
| Sunday | 9am - 5pm |