Tocha Communications

Tocha Communications

Share

Photos from Tocha Communications's post 01/06/2026

‎የቶጫ ወረዳ ማህበረሰብ ክፍሎች በሁሉም ምርጫ ጣቢያ ማልደዉ ወጥተዉ እየመረጡ ይገኛሉ
‎*****************

‎ዛሬ ግንቦት 24 ቀን በመላው የሀገሪቱ ክፍሎች የሚገኙ ዜጎች የወደ ፊት እጣ ፈንታቸውን ለመወሰን ይህንን ታሪካዊ 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ለማካሄድና የዲሞክራሲያዊ ስርዓት ግንባታቸውን ለማፅናት በነቂስ ወጥተው እየመረጡ ይገኛሉ።

‎በዳዉሮ ዞን ቶጫ ወረዳ ነዋሪዎች በማለዳው ቅዝቃዜ ሳይበግራቸው በዬ ምርጫ ጣቢያ ቀድመው በመገኘት ታሪካዊ አሻራቸውን ለማሳረፍና ለመምረጥ ካርዳቸዉን ይዘዉ እየመረጡና ለመምረጥ ሰልፍ ላይ ይገኛሉ።

‎በዚህ የምርጫ ጣቢዎች ሂደቱ ስኬታማና ምቹ እንዲሆን ሰፊ ዝግጅት ተደርጓ። መራጮች ወደ ምርጫ ጣቢያው ሲያቀኑ ያለምንም እንግልት ድምጻቸውን መስጠት እንዲችሉ የድምፅ መስጫ ቦታ እና ሳጥኖችን ጨምሮ ሌሎች አስፈላጊ የቁሳቁስ ዝግጅቶች በሚገባ ተሟልተው ድምፅ የመስጠት ስራ በስከት ቀጥሏል።

‎ቶጫ ኮሙዩኒኬሽን !

Photos from Tocha Communications's post 01/06/2026

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር) ድምፃቸውን ሰጡ

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር) በሚወዳደሩበት የምርጫ ክልል በመገኘት ድምፃቸውን ሰጥተዋል።

ርዕሰ መስተዳድሩ የገዥውን የብልፅግና ፓርቲን ወክለው ለክልሉ ምክር ቤት አባልነት እየተወዳደሩ እንደሚገኙ የታወቀ ሲሆን፣ ዛሬ ማለዳ ላይ በተመረጡበት የምርጫ ክልል በመገኘት ነው የመምረጥ መብታቸውን የተጠቀሙት።

ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር) ድምፃቸውን ከሰጡ በኋላ ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ፤ የክልሉ ህዝቦች በነቂስ ወጥተው በያዙት የመራጭነት ካርድ ለቀጣይ የዕድገትና የተሻለች አገር የሚበጃቸውንና የሚወክላቸውን ፓርቲ እንዲመርጡ ጥሪ አቅርበዋል።

በክልሉ እየተካሄደ ባለው በዚህ ምርጫ ህዝቡ በከፍተኛ መነሳሳት ድምፅ እየሰጠ እንደሚገኝና ሂደቱም በሰላማዊ ሁኔታ እየተከናወነ መሆኑ ተገልጿል ሲል የዘገበው SWMN ነው።

Photos from Tocha Communications's post 26/05/2026

በቶጫ ወረዳ ቦብ ቀበሌ የሰላም ምልክት የሆነው ነጭ ባንዲራ የማሰቀል ስነ-ስርዓት ተካሄደ

‎በዳዉሮ ዞን ቶጫ ወረዳ ቦብ ቀበሌ የዘላቂ ሰላምን አስፈላጊነት ለማብሰር እና የህብረተሰቡን አንድነት ለማጠናከር ያለመ የሰላም ምልክት ነጭ ባንዲራ የመስቀል ስነ-ስርዓት በድምቀት ተካሂዷል።

‎በስነ-ስርዓቱ ላይ የተገኙት የቶጫ ወረዳ ፖሊስ አዛዥ ም/ኮን/ር ታሪኩ ከበደ ባስተላለፉት መልዕክት፣ ሰላም ለማንኛውም ልማትና እድገት መሰረት መሆኑን አንስተዋል

‎አክለዉም፦ዛሬ የሰቀልነው ነጭ ባንዲራ ተራ ጨርቅ ሳይሆን የወረዳችንን ህዝብ የሰላም ጥማት፣ አብሮነትና እርቅን የሚያሳይ ትልቅ ምልክት መሆኑን በማንሳት ፖሊስ ከህዝቡ ጋር በመቀናጀት ይሄንን ሰላም የማስከበርና የማስቀጠል ስራውን አጠናክሮ እንደምቀጥል አብራርተዋል።

‎የወረዳው ፖሊስ ጽህፈት ቤት የወንጀል መከላከል ዘርፍ ኃላፊ ም/ኢንስፔክተር መብራቱ አደለ ፦ በበኩላቸው፣ ወንጀልን ቀድሞ ለመከላከልና አስተማማኝ ፀጥታ ለመፍጠር የህብረተሰቡ ተሳትፎ ወሳኝ መሆኑን ጠቁመዉ ይህ የሰላም ባንዲራ መውለብለብም እያንዳንዱ የህብረተሰብ ክፍል ለቀበሌው ሰላም የበኩሉን ጠባቂ እንዲሆን ትልቅ የቤት ስራ የሚጥል መሆኑን አብራርተዋል።

‎የወረዳ ፋይናንስ ኢኮኖሚ ል/ጽ/ቤት ም/ኃ አቶ ታሪኩ አለማየሁ እንደጠቆሙት ፦የአካባቢው መረጋጋት ለህዝቡ እለታዊ የልማትና የንግድ እንቅስቃሴዎች መሳካት ቁልፍ ሚና እንዳለው በማንሳት መንግስት ከአካባቢው ማህበረሰብ ጋር በመሆን የጀመራቸውን የሰላም አማራጮች አጠናክሮ እንደሚቀጥልም አረጋግጠዋል።

‎በመጨረሻም የቦብ ቀበሌ ፖሊስ አስተባባሪ ም/ሳጅን ዳንኤል ደሱላ እንደጠቆሙት ፦በቀበሌው ደረጃ ህዝባዊ የፀጥታ መዋቅሩን በማጠናከር ከህዝቡ ጎን በመቆም የተገኘውን ሰላም ዘላቂ ለማድረግ ሌሊትና ቀን እንደሚሰሩ ቃል ገብተዋል።

‎በእለቱ የነጭ ባንዲራ ማውለብለብ ስነ-ስርዓቱ ሲከናወን የአካባቢው ነዋሪዎች፣ የሃገር ሽማግሌዎችና ወጣቶች የተገኙ ሲሆን፣ የተፈጠረውን ሰላም በጋራ ለመጠበቅና ለመንከባከብ ያላቸውን ዝግጁነት በመግለጽ በቀበሌዉ የሠላም አምባሳደር ለሆኑት ለአቶ መለሰ መኩሪ ህዝቡ እዉቅና በመስጠት መድረኩ ተጠናቅቋል።

‎ዘገባዉ የቶጫ ወረዳ መንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት ነዉ።

Photos from Tocha Communications's post 23/05/2026

‎የቶጫ ወረዳ ፖሊስ ጽ/ቤት ከባለ ሁለት እግር ሞተር አሽከርካሪዎች እና ከባጃጅ ሾፈሮች ጋር በወቅታዊ ነባራዊ ሁኔታዎች ላይ ያቶከረ ዉይይት ማካሄዱ ተገለጸ።

‎ግንቦት 15/9/2018 ዓ/ም ቶጫ ወረዳ መንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት።

‎የቶጫ ወረዳ ፖሊስ ጽ/ቤት ከባለ ሁለት እግር ሞተር አሽከርካሪዎች እና ከባጃጅ ሾፈሮች ጋር በወቅታዊ ነባራዊ ሁኔታዎች ላይ ያቶከረ ዉይይት አካሂዷል ።

‎በዉይይቱ ላይ የተለያዩ ትራፍክ አደጋ መከላከያ ግንዛቤ ተሰጥቶ ከታርፍ በላይ ማስከፈልና ትርፍ መጫን ፣ሰዓት ዕላፍ ማሽከርከር ዙሪያ ላይ ሰፋ ያለ ዉይይት ተደርጎበታል ።

‎በዉይይት መድረክ ላይ የዳዉሮ ዞን ፖሊስ መምሪያ ከፍተኛ ባሙያን ጨምሮ የወረዳዉ ፖሊስ ማኔጅመንት አካላት ተሳትፈዋል።

‎ቶጫ ወረዳ መንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት።

Want your organization to be the top-listed Government Service in Toamasina?
Click here to claim your Sponsored Listing.

Telephone

Website

Address

Tocha
Toamasina