Arsenal fan
11/06/2026
አሜሪካ እንዳይገባ የታገደው ሶማሊያዊ ዳኛ የአውሮፓ ሱፐር ካፕ የፍጻሜ ጨዋታን እንዲመራ ተመረጠ
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 4፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) አሜሪካ እንዳይገባ የታገደው ሶማሊያዊ የዓለም ዋንጫ ዳኛ ኦማር አርታን የአውሮፓ ሱፐር ካፕ የፍጻሜ ጨዋታን እንዲመራ ተመርጧል፡፡
አሜሪካ፣ ካናዳ እና ሜክሲኮ ባዘጋጁት በ2026 የዓለም ዋንጫ አሜሪካ እንዳይገባ የተከለከለው የ34 ዓመቱ ዳኛ የአውሮፓ ሱፐር ካፕ የፍጻሜ ጨዋታን እንዲመራ መመረጡ ተመላክቷል፡፡
የአውሮፓ ሱፐር ካፕ የፍጻሜ ጨዋታ በአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ አሸናፊው ፒኤስጂ እና በዩሮፓ ሊግ አሸናፊው አስቶን ቪላ መካከል የሚደረግ ይሆናል፡፡
የዓለም ዋንጫ ጨዋታዎችን በዳኝነት እንዲመራ ተመርጦ አሜሪካ እንዳይገባ የታገደው ሶማሊያዊ ዳኛ ኦማር አርታን ወደ ሀገሩ ሲመለስ ደማቅ አቀባበል እንደተደረገለት ይታወቃል፡፡
30/05/2026
አርሰናል 1 0 PSG
Ht
Want your business to be the top-listed Media Company in Awassa?
Click here to claim your Sponsored Listing.
Click here to claim your Sponsored Listing.
Category
Website
Address
Awassa