WMCC
(WMCC) is a broadcast media company based in Addis Ababa, the political capital of Africa. The company which owns TV and Radio Stations aspires to become a pan African media company currently disseminating information in local and international languages. Walta has built its reputation through covering all aspect of Ethiopia and beyond in its professional news, documentary and programs reporting.
13/04/2026
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) ለላይቤሪያ ፕሬዚዳንት አቀባበል አደረጉ
አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 5፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ለላይቤሪያ ፕሬዚዳንት ጆሴፍ ንዩማ ቦአካይ አቀባበል አድርገዋል።
የላይቤሪያ ፕሬዚዳንት ጆሴፍ ንዩማ ቦአካይ ለይፋዊ የሥራ ጉብኝት ዛሬ ምሽት አዲስ አበባ ገብተዋል፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) በማሕበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት ጽሑፍ ÷ ፕሬዚዳንት ጆሴፍ ንዩማ ቦአካይ የነገ ብሩህ ተስፋ እየተሰራባት ወደ ምትገኘው ምድረቀደምት ኢትዮጵያ እንኳን በሰላም መጡ ብለዋል።
በቆይታዎ እጅግ ፍሬያማ ወይይት እንደሚኖረን እምነቴ ነው ሲሉም ገልጸዋል።
13/04/2026
በጎሮ ጉቱ ወረዳ በትራፊክ አደጋ የ9 ሰዎች ሕይወት አለፈ
አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 5፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በኦሮሚያ ክልል ምስራቅ ሐረርጌ ዞን ጎሮ ጉቱ ወረዳ በደረሰ የትራፊክ አደጋ የዘጠኝ ሰዎች ሕይወት አልፏል።
አደጋው ከአዲስ አበባ ወደ ድሬዳዋ ከተማ ሲጓዝ በነበረ ኮንቴነር የጫነ ተሽከርካሪ ላይ መድረሱን የዞኑ ፖሊስ መምሪያ አስታውቋል፡፡
በተከሰተው አደጋም እስካሁን የዘጠኝ ሰዎች ሕይወት ማለፉ ነው የተገለጸው፡፡
13/04/2026
በአማራ ክልል የተለያዩ አካባቢዎች ለ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ እየተካሄደ ያለው የመራጮች ምዝገባ በምስል፡-
13/04/2026
ሸገር ከተማ እና ነገሌ አርሲ አቻ ተለያዩ
13/04/2026
በሲቢኢ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ዛሬ አራት ጨዋታዎች ይደረጋሉ
በሲቢኢ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ዛሬ አራት ጨዋታዎች ይደረጋሉ
አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 5፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ27ኛው ሳምንት ሲቢኢ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር ዛሬ አራት ጨዋታዎች ይደረጋሉ።
ቀን 7 ሰዓት በአበበ ቢቂላ ስታዲየም ሸገር ከተማ እና ነገሌ አርሲ የሚገናኙ ሲሆን÷ በተመሳሳይ ስታዲየም ቀን 10 ሰዓት ላይ አርባ ምንጭ ከተማ እና ቅዱስ ጊዮርጊስ ጨዋታቸውን ያደርጋሉ።
የሊጉ መርሐ ግብር ቀጥሎ ሲካሄድ ቀን 9 ሰዓት ላይ መቐለ 70 እንደርታ ከወልዋሎ ዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ይገናኛል።
እንዲሁም በተመሳሳይ ስታዲየም አመሻሽ 12 ሰዓት ላይ ሀዋሳ ከተማ እና ምድረ ገነት ሽረ ጨዋታቸውን ያደርጋሉ።
13/04/2026
የኢትዮጵያ የኢንዱስትሪ ጉዞ አዲስ ምዕራፍ እየተራመደ ይገኛል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን ጋር ባደረጉት የሁለት ክፍሎች ቃለምልልስ ኢትዮጵያ የአዲሱ ዘመን የኢንዱስትሪ መስፋፋትን እንዴት እየበየነች እንደሆነ አብራርተዋል።
የመጀመሪያውን ክፍል ማክሰኞ ሚያዚያ 6 ቀን 2018 ዓ.ም ከምሽቱ 2:30 ይጠብቁ።
Click here to claim your Sponsored Listing.