Tourism Training Institute
Providing skill-based and up to the standard
pre and on job training both in terms of
theory and practice to foster the
development of the tourism and hotel
sector.
2. Offering short, medium, and long-term
professional development training to
employees, leaders, and service providers in
the hotel and tourism sector.
3. Supporting the overall socio-economic
development endeavor of the coun
22/06/2026
“ያለ ጥናትና ምርምር መሪነት የሚከናወን ሥራ፤ በጨለማ በድፍረት እንደ መጓዝ ነው” አቶ ይታሰብ ስዩም
ቱ ማ ኢ
ሰኔ 15 ቀን 2018 ዓ.ም
የፌዴራል ቱሪዝም ማሰልጠኛ ኢንስቲትዩት ተቋማዊ እድገቱን ይበልጥ ለማጠናከር ያለመና በበጀት ዓመቱ በአሰልጣኞቹና ተመራማሪዎቹ የተሰሩ አጠቃላይ የጥናትና ምርምር ሥራዎች ይፋ የተደረጉበት የምርምር መድረክ እየተካሄደ ነው።
ይህ መድረክ የተቋሙ አንጋፋ አሰልጣኞችና ተመራማሪዎች በቱሪዝም እና ሆስፒታሊቲ ዘርፍን ላይ ያሉ አሰራሮችን ለማዘመንና ውጤታማነታቸውን ለማሳደግ ታስበው የተሰሩ 6 (ስድስት) መሠረታዊና ከተግባራዊ ሥራ ጋር የተገናኙ የምርምር ሥራዎቻቸውን የሚቀርብበት ነው።
የምርምር መድረኩን በንግግር የከፈቱት የጥናትና ምርምር ዘርፍ ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ ይታሰብ ስዩም፤ በማንኛውም ተቋማዊ ዕድገት ውስጥ በማስረጃና በምክንያት ላይ የተመሰረቱ ጥናቶች ያላቸውን ምትክ የሌለው ሚና አጽንኦት ሰጥተው አብራርተዋል።
“ማንኛውንም የአሠራር ማዕቀፍ ሁለንተናዊ ከሆነ የጥናትና ምርምር መሪነት ውጭ ለመተግበር መሞከር በጨለማ ውስጥ በድፍረት እንደመጓዝ ይቆጠራል” ያሉት አቶ ይታሰብ፤ “በአሁኑ ዘመናዊ ማኅበረ-ኢኮኖሚያዊ እውነታ ውስጥ፣ ተቋማዊ ተልእኮዎችን ያለ ጥልቅና ሳይንሳዊ ምርምር ለማሳካት መሞከር በፍጹም አማራጭ ሊሆን አይችልም” ሲሉ ገልጸዋል።
ይፋ የተደረጉት ስድስቱም የምርምር ሥራዎች ሙሉ በሙሉ በተቋሙ የውስጥ አሰልጣኝ ተመራማሪዎች የተሰሩ በመሆናቸው፤ ግኝቶቹ በቀጥታ እውነታውን መሠረት ያደረጉና ተግዳሮቶችን የሚፈቱ ናቸው ተብሎ ይጠበቃል።
መርሃ ግብሩ ኢንስቲትዩቱ ጥራት ያለው ስልጠና ከመስጠት ባለፈ፤ ለዘርፉ የዕውቀት ምንጭና የምርምር ማዕከል የመሆን አቅሙ እያደገ መምጣቱን የሚያሳይ ነው ተብሏል።
በዚህ የጥናትና ምርምር መድረክ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶችና ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል።
ትክክለኛ መረጃዎችን ለማግኘት የሚከተሉትን ማስፈንጠሪያዎች ይጠቀሙ
ፌስቡክ፡ https://www.facebook.com/tticommunication
ቴሌግራም ፡https://t.me/tticommunication
http://tiktok.com/
በአዲስ አበባ በሚገኙ የቱሪስት መዳረሻ ሥፍራዎች የኢንስቲትዩቱ ሰልጣኞች ትምህርታዊ ጉብኝት
28/05/2026
የኢንስቲትዩቱ ሰልጣኞች በአንድነት ፓርክ እና በብሔራዊ ቤተመንግሥት፤
ቱ.ማ.ኢ
ግንቦት 20/2018 ዓ.ም
የፌዴራል ቱሪዝም ማሰልጠኛ ኢንስቲትዩት በየዓመቱ የቱሪዝም ትምህርት ክፍል ሰልጣኞች በንድፈሃሳብ የቀሰሙትን እውቀት በተግባር ለመደገፍ የሚያስችል ትምህርታዊ ጉብኝት ከሚወስዱባቸው መዳረሻዎች ለህዝብ ክፍት የተደረጉት አንድነት ፓርክና ብሔራዊ በተመንግስት ይጠቀሳሉ፡፡
እነዚህ መዳረሻዎች አዲስ አበባ ከተማ ከሚገኙ የታሪክ፣ የተፈጥሮና የባህል ቅርሶችን የያዙ በመሆናቸው ለሰልጣኞቻችን ጥሩ እድል ፈጥሯል ያሉት የጉብኝቱ አስተባባሪና የቱሪዝም ትምህርት ክፍል ኃላፊ አቶ ሲሳይ አብርሃም ናቸው፡፡
አቶ ሲሳይ ስለጉብኝቱ ዓላማ ሲገልጹ ሰልጣኞች ተግባራዊ እውቀት በመቅሰም የሀገራችንን ታሪካዊ፣ ባህላዊ እና ተፈጥሯዊ የቱሪስት መስህቦች አያያዝና አደረጃጀት በቅርብ እንዲረዱ ማስቻል፤ በፓርኮችና በቱሪስት መዳረሻ ሥፍራዎች የሚሰጡ አገልግሎቶችን በተግባር ማየትና ያሉ ከክፍተቶች በስልጠና መግደገፍ እንዲሁም የዘርፉን ተወዳዳሪነት ለማሳደግ ነገ የኢትዮጵያን ቱሪዝም ለዓለም የሚያስተዋውቁ ብቁ ባለሙያዎችን ማፍራት ነው ብለዋል፡፡
በጉብኝቱ ወቅት ሰልጣኞቹ የሀገሪቱን አስደናቂ ታሪካዊ ቅርሶች፣ የተፈጥሮ ሃብቶች እና የቤተመንግሥቱን ልዩ የስነ-ህንጻ ጥበብ በጥልቀት የተመለከቱ ሲሆን ይህም ለቀጣይ ሙያዊ ጉዟቸው ትልቅ መነሳሳትን የፈጠረ መሆኑን ገልጸዋል።
ትክክለኛ መረጃዎችን ለማግኘት የሚከተሉትን ማስፈንጠሪያዎች ይጠቀሙ
ፌስቡክ፡ https://www.facebook.com/tticommunication
ቴሌግራም ፡https://t.me/tticommunication
http://tiktok.com/
Click here to claim your Sponsored Listing.
Category
Website
Address
Addis Ababa
4350