Fidel Tube

Fidel Tube

Share

Photos from Fidel Tube's post 02/12/2020

በመቀሌ ከተማ የአገር መከላከያ ሰራዊት የማያውቀው የመሳሪያ ማከማቻ ዲፖ ተገኘ

የልዩ ዘመቻ 2ኛ ብርጌድ 3ኛ ሬጅመንት አዛዥ ሌተናል ጀነራል ሳድቅ አህመድ እንዳሉት መቀሌ ላይ መከላከያ የማያወቀው የመሳሪያ ማከማቻ ዲፖ ተገኝቷል።

የጁንታው ቡድን ውጊያውን መቋቋም ሲሳነው ትጥቁን እያራገፈ ፈርጥጧልም ብለዋል።

ከዚህ ውስጥ ሰራዊቱ የማያውቀው የተለያዩ የጦር መሳሪያዎች የተከማቹበት ዲፖ ተገኝቷል ብለዋል

የሰሜን እዝ አመራሮችን ጠይቀን ስለዲፖው እንደማያውቁ ገልጸውልናል ያሉት ሌተናል ጀነራሉ፤ በቀጣይም ተመሳሳይ የመሳሪያ ማከማቻወችም ሊገኙ እንደሚችሉ ገልፀዋል።

በመሆኑም እነዚህ ከቀላል እስከ ቡድን መሳሪያዎች ወንጀል እዳይፈጸምባቸው የፍተሻ ስራው ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል።
ኢዜአ

Ethiopian Body builder Tsega Worku 27/05/2020

Ethiopian Body builder Tsega Worku Full Body at Home Workout ቤታችን ውሥጥ መስራት የምንችለው ቀለል ያለ እስፖርት

Photos from Fidel Tube's post 22/05/2020

በኢትዮጲያ 30 ተጨማሪ ሰዎች ላይ የኮሮና ቫይረስ ተገኘባቸው‼️

በአጠቃላይ በኮሮና ቫይረስ የተያዙ ሰዎች ቁጥር 429 ደርሷል፡፡

የታማሚዎች ዝርዝር ሁኔታ፡-⬇️

~ ባለፉት 24 ሰዓት ዉስጥ ለ3645 ሰዎች ምርመራ ተደርጎ 30 ኢትዮጲያዉያን ላይ ቫይረሱ ተገኝቷል፡፡

~ 26ቱ ወንዶች ሲሆኑ 4ቱ ደግሞ ሴት ናቸው።እድሜያቸዉ ከ15 እስከ 60 ዓመት የሆኑ ናቸዉ።

~ የመኖሪያ ስፍራቸዉ 18 ሰዎች ከአዲስ አበባ፣4 ሰዉ ከአሮሚያ ክልል(ጅግጅጋ ለይቶ ማቆያ )፣ 3 ሰዎች ከአፋር ክልል ፣3 ሰዉ ከትግራይ ክልል፣2 ሰዉ ድንበር ተሻጋሪ አሽከርካሪ

~ 9 ሰዎች የውጭ ሀገራት የጉዞ ታሪክ ያላቸው ናቸው፡፡

~ 17 ሰዎች በበሽታው ከተያዘ ሰው ጋር ግንኙነት አላቸዉ፡፡

~ የውጭ ሀገር የጉዞ ታሪክና በበሽታው ከተያዘ ሰው ጋር ግንኙነት የሌላቸዉ 4 ሰዎች ናቸው።

ተጨማሪ መረጃ ፦

~ አጠቃላይ ምርመራ የተደረገላቸው ሰዎች ቁጥር 73,164 ደርሷል።

~ ባለፉት 24 ሰዓት ውስጥ 5 ሰዎች አገግሟል።

~ አጠቃላይ ያገገሙ ግለሰቦች 128 ደርሰዋል።

~ በጽኑ ህሙማን ማከምያ ዉስጥ የሚገኝ ታማሚ የለም ፡፡

~ በለይቶ ህክምና ውስጥ ያሉ 294 ናቸው።

~ የአምስት ሰዎች ህይወት አልፏል፡፡

21/04/2020

በኢትዮጵያ ተጨማሪ 3 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው ተረጋገጠ!

በኢትዮጵያ ባለፋት 24 ሰዓት ውስጥ በተደረገ 745 የላብራቶሪ ምርመራ ሶስት (3) ሰዎች በኮሮና ቫይረስ መያዛቸውን ተረጋግጧል። በአጠቃላይ በሀገራችን በቫይረሱ የተያዙ ሰዎች ቁጥር 114 ደርሷል።

የታማሚዎች ዝርዝር ሁኔታ ፦

ታማሚ 1 - የ42 ዓመት ቻይናዊ የመኖሪያ ቦታው ሰበታ ዞን ፤ የውጭ ሀገር የጉዞ ታሪክ የለውም፤ በበሽታው ከተያዘ ሰው ጋር ያለው ግንኙነት በመጣራት ላይ ነው።

ታማሚ 2 - የ22 ዓመት ኢትዮጵያዊ የአዲስ አበባ ከተማ ነዋሪ፤ የውጭ ሀገር የጉዞ ታሪክ የለውም፤ በስራው ባህሪ ለበሽታው ተጋላጭነት ያለው።

ታማሚ 3 - የ22 ዓመት ኢትዮጵያዊ የአዲስ አበባ ከተማ ነዋሪ፤ ከሳዑዲ የመጣና በለይቶ ማቆያ ውስጥ ያለ።

Want your business to be the top-listed Media Company in Addis Ababa?
Click here to claim your Sponsored Listing.

Category

Website

Address

Addis Ababa

Opening Hours

00:00 - 12:00