Mercy Reformed Church

Mercy Reformed  Church

Share

19/08/2023

በምድርም የሚኖሩ ሁሉ እንደ ምናምን ይቈጠራሉ፤ በሰማይም ሠራዊት በምድርም ላይ በሚኖሩ መካከል እንደ ፈቃዱ ያደርጋል፤ እጁንም የሚከለክላት ወይም፦ ምን ታደርጋለህ? የሚለው የለም።
ዳን 4፡34

በህይወታችን በየእለቱ የምናየው የምናስተውለው እንዲሁም የማናየው የማናውቀውም የተለያዩ ብዙ ነገሮኖች ይደረጋሉ ፤ ሰይጣን ያደረገው በሚመስለን ስንራገም (ስንገስጽ) ፤ እኛ ራሳችን ያረግነው በሚመስለን ደግሞ አንዳንዴ ተጸጽተን ንሥሀ ሥንገባ እና ሌላ ጊዜ ደሞ ራሳችንን ስናሞካሽ ፣ እግዚአብሔር አርጎታል ብለን ባሰብናቸው ነገሮች ደሞ ስናመስግን ፣ አንዳንዴም .. ግን እውነት እግዚአብሔር ይወደኛል ? እያልን ፍቅሩን ጥያቄ ውስጥ ሥንከት እና ማመስገን ሲያቅተን እንገኛለን ...ሌላም ሌላም ... ፤
ሆኖም እግዚአብሔር ለጠራቸው ሁሉ አሁን ያሉበት ሁኔታ ምንም ይሁን ምን " ......ነገር ሁሉ ተያይዞ ለበጎ እንዲሠራ እንደሚያደርግላቸው እናውቃለን "። ሮሜ 8:28

02/07/2022

ከሁሉም በላይ ልብህን ጠብቅ፤ የሕይወት ምንጭ ነውና።
ምሳሌ 4:23

07/06/2022

እነሆ፥ እኔ ወራዳ ሰው ነኝ፤
ኢዮ 40:4

ኢዮብ "ወራዳ ነኝ " ያለው ኃጢአተኝነቱን ተገንዝቦ ነው ። ምናልባት ስለ ራስህ ያለህ ግንዛቤ ኢዮብ ሥለ ራሡ ከተገነዘበው፣ ከተሰማው፣ ካመነበት የተለዬ ከሆነ እይታህ ልክ አይደለም ራስህን እያታለልክ ነው (1ዮሐ 1፡8) አሊያ ኃጢአትህን ተናዘህ ከእግዚአብሔር ጋር ተወዳጅተሐል ማለት ነው ። ኢዮብ ከሠዎች አንጻር ዕድቁ የተመሰከረለት አጠገቡ ካሉት ሠወች በላይ የተመሰገነ ሠው ነው፤ (ኢዮ 1፡1) ነገር ግን እንከን አልባ በሆነው በእግዚአብሔር የፍርድ ወንበር ፊት ማን ልክ ነኝ ማለት ይችላል? ( መዝ 143፡2) በርግጥ ይህ ነገር የገባው ኢዮብ ብቻ አይደለም አነ ዳዊት ፣ ኢሳያስ፣ ጳውሎስም ተመሳሳይ ነገር ብለዋል።

ጌታ ኢየሱስ ኃጢአተኞችን ሊፈልግና ሊያድን መጥቷል (ሉቃ 19:10) እርሱ ኃጢአተኞችን እንጂ ፃድቃንን ልጠራ አልመጣሁም ብሏልና (ማቴ 9፡13) ኃጢአተኛ መሆንህን ካመንህ ጥሪውን ተቀበል ፤ አሁን የተወደደ የመዳን ሰዓት ነው (2 ቆሮ 6፡2) ። ማንም አድነኝ ለማለት እድል የማያገኝበት ሌሊት ይመጣል (ዮሐ 9፡4)። አሁን ግን ከኃጢአት ኃይልና ቅጣት የሚያድን የእግዚአብሔር ፀጋ ተገልጧልና ( ቲቶ 2፡11) መንግስተ ሰማይም ቀርባለችና ንሥሐ ግባ ( ማቴ 3፡1)።
ታላቁን የመዳን ጥሪ ቸል አትበል !!!!!

👇👇👇👇👇👇👇👇👇2 ቆሮ 5፡ 20

04/06/2022

መልካም ማድረግን ለሌሎችም ማካፈልን አትርሱ፤ እንዲህ ያለው መሥዋዕት እግዚአብሔርን ደስ ያሰኘዋልና።
ዕብ 13፡16

Want your place of worship to be the top-listed Place Of Worship in Addis Ababa?
Click here to claim your Sponsored Listing.

Telephone

Website

Address

Addis Ababa

Opening Hours

09:00 - 17:00