Mercy Reformed Church
19/08/2023
በምድርም የሚኖሩ ሁሉ እንደ ምናምን ይቈጠራሉ፤ በሰማይም ሠራዊት በምድርም ላይ በሚኖሩ መካከል እንደ ፈቃዱ ያደርጋል፤ እጁንም የሚከለክላት ወይም፦ ምን ታደርጋለህ? የሚለው የለም።
ዳን 4፡34
በህይወታችን በየእለቱ የምናየው የምናስተውለው እንዲሁም የማናየው የማናውቀውም የተለያዩ ብዙ ነገሮኖች ይደረጋሉ ፤ ሰይጣን ያደረገው በሚመስለን ስንራገም (ስንገስጽ) ፤ እኛ ራሳችን ያረግነው በሚመስለን ደግሞ አንዳንዴ ተጸጽተን ንሥሀ ሥንገባ እና ሌላ ጊዜ ደሞ ራሳችንን ስናሞካሽ ፣ እግዚአብሔር አርጎታል ብለን ባሰብናቸው ነገሮች ደሞ ስናመስግን ፣ አንዳንዴም .. ግን እውነት እግዚአብሔር ይወደኛል ? እያልን ፍቅሩን ጥያቄ ውስጥ ሥንከት እና ማመስገን ሲያቅተን እንገኛለን ...ሌላም ሌላም ... ፤
ሆኖም እግዚአብሔር ለጠራቸው ሁሉ አሁን ያሉበት ሁኔታ ምንም ይሁን ምን " ......ነገር ሁሉ ተያይዞ ለበጎ እንዲሠራ እንደሚያደርግላቸው እናውቃለን "። ሮሜ 8:28
02/07/2022
ከሁሉም በላይ ልብህን ጠብቅ፤ የሕይወት ምንጭ ነውና።
ምሳሌ 4:23
እነሆ፥ እኔ ወራዳ ሰው ነኝ፤
ኢዮ 40:4
ኢዮብ "ወራዳ ነኝ " ያለው ኃጢአተኝነቱን ተገንዝቦ ነው ። ምናልባት ስለ ራስህ ያለህ ግንዛቤ ኢዮብ ሥለ ራሡ ከተገነዘበው፣ ከተሰማው፣ ካመነበት የተለዬ ከሆነ እይታህ ልክ አይደለም ራስህን እያታለልክ ነው (1ዮሐ 1፡8) አሊያ ኃጢአትህን ተናዘህ ከእግዚአብሔር ጋር ተወዳጅተሐል ማለት ነው ። ኢዮብ ከሠዎች አንጻር ዕድቁ የተመሰከረለት አጠገቡ ካሉት ሠወች በላይ የተመሰገነ ሠው ነው፤ (ኢዮ 1፡1) ነገር ግን እንከን አልባ በሆነው በእግዚአብሔር የፍርድ ወንበር ፊት ማን ልክ ነኝ ማለት ይችላል? ( መዝ 143፡2) በርግጥ ይህ ነገር የገባው ኢዮብ ብቻ አይደለም አነ ዳዊት ፣ ኢሳያስ፣ ጳውሎስም ተመሳሳይ ነገር ብለዋል።
ጌታ ኢየሱስ ኃጢአተኞችን ሊፈልግና ሊያድን መጥቷል (ሉቃ 19:10) እርሱ ኃጢአተኞችን እንጂ ፃድቃንን ልጠራ አልመጣሁም ብሏልና (ማቴ 9፡13) ኃጢአተኛ መሆንህን ካመንህ ጥሪውን ተቀበል ፤ አሁን የተወደደ የመዳን ሰዓት ነው (2 ቆሮ 6፡2) ። ማንም አድነኝ ለማለት እድል የማያገኝበት ሌሊት ይመጣል (ዮሐ 9፡4)። አሁን ግን ከኃጢአት ኃይልና ቅጣት የሚያድን የእግዚአብሔር ፀጋ ተገልጧልና ( ቲቶ 2፡11) መንግስተ ሰማይም ቀርባለችና ንሥሐ ግባ ( ማቴ 3፡1)።
ታላቁን የመዳን ጥሪ ቸል አትበል !!!!!
👇👇👇👇👇👇👇👇👇2 ቆሮ 5፡ 20
04/06/2022
መልካም ማድረግን ለሌሎችም ማካፈልን አትርሱ፤ እንዲህ ያለው መሥዋዕት እግዚአብሔርን ደስ ያሰኘዋልና።
ዕብ 13፡16
Click here to claim your Sponsored Listing.
Category
Telephone
Website
Address
Opening Hours
| 09:00 - 17:00 |