Amaizing GRACE
16/10/2025
#ትንቢቱ #ሲፈጸም
“ስለዚህም እርሱ ብዙዎችን ይወርሳል፥ ከኃያላንም ጋር ምርኮን ይከፋፈላል፤ ነፍሱን ለሞት አሳልፎ ሰጥቶአልና፥ ከዓመፀኞችም ጋር ተቈጥሮአልና እርሱ ግን የብዙ ሰዎችን ኃጢአት ተሸከመ፥ ስለ ዓመፀኞችም ማለደ።”
— ኢሳይያስ 53፥12
1. ነፍሱን ለሞት አሳልፎ ሰጥቶአልና 👇
“ኢየሱስም በታላቅ ድምፅ ጮኸ ነፍሱንም ሰጠ።”
— ማርቆስ 15፥37
“ኢየሱስም ሆምጣጤውን ከተቀበለ በኋላ፦ ተፈጸመ አለ፥ ራሱንም አዘንብሎ ነፍሱን አሳልፎ ሰጠ።”
— ዮሐንስ 19፥30
2. ከአመጸኞችም ጋር ተቆጥሮአልና 👇
ከእርሱም ጋር ሁለት ወንበዶች አንዱን በቀኙ አንዱንም በግራው ሰቀሉ። መጽሐፍም፦ ከአመፀኞች ጋር ተቆጠረ ያለው ተፈጸመ።
---ማርቆ 15:27-28
3. ስለ አመጸኞችም ማለደ 👇
ሉቃስ 23:33-34
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
³³ ቀራንዮም ወደሚባል ስፍራ በደረሱ ጊዜ፥ በዚያ እርሱን ክፉ አድራጊዎቹንም አንዱን በቀኝ ሁለተኛውንም በግራ ሰቀሉ።
³⁴ ኢየሱስም፦ አባት ሆይ፥ የሚያደርጉትን አያውቁምና ይቅር በላቸው አለ። ልብሱንም ተካፍለው ዕጣ ተጣጣሉበት።
👉ብዙዎችን ይወርሳል እንደተባለም በሞቱና በትንሳኤው በክርስቶስ የምናምነውን እኛን የራሱ አድርጎናል። ወርሶናል። በአለም ላይ ያሉ በእርሱ ያመኑ ወንድሞቻችንና እህቶቻችን በእርሱ ተወርሰዋል። በነፍሱ የገዛን የእርሱ ተከታዮች ነን። እርሱን አምነን ተከትለነዋል። እርሱም የዘላለም ህይወት ሰጥቶናል። ለዘላላምም አንጠፋም። 👇
ዮሐንስ 10
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
²⁷ በጎቼ ድምፄን ይሰማሉ እኔም አውቃቸዋለሁ ይከተሉኝማል፤
²⁸ እኔም የዘላለም ሕይወትን እሰጣቸዋለሁ፥ ለዘላለምም አይጠፉም፥ ከእጄም ማንም አይነጥቃቸውም።
²⁹ የሰጠኝ አባቴ ከሁሉ ይበልጣል፥ ከአባቴም እጅ ሊነጥቃቸው ማንም አይችልም።
Please ይህን እውነት Share አድርጉት። 🙏🙏
10/07/2025
#በዘሬ #አይግባ #ያልኩት (ዘማሪ ኤልያስ አብጤ)
ኦርጅናል መዝሙሩ ነው ሊንኩን ተጭናችሁ ስሙት። በዛውም ሰብስክራይብ በማድረግ ይተባበሩን።
በዘሬ አይግባ ያልኩት/Singer Elias Abeta “ያዳነን በቅዱስም አጠራር የጠራን እግዚአብሔር ነውና፥ ይህም እንደ ራሱ አሳብና ጸጋ መጠን ነው እንጂ እንደ ሥራችን መጠን አይደለም፤ ይህም ጸጋ ከዘላለም ዘመናት በፊት በክርስቶስ ኢየ...
Click here to claim your Sponsored Listing.